דילוג לתוכן המרכזי בעמוד

ספר החודש

በለስየተሞላቅርጫት

በ: ኡሪ አሎን ምሳሌዎች: ምናሔም ሃልበርስታድት

አድሪያኑስ ቄሳር አንድ ሽማግሌ ለምን በለስን እንደሚተክለው አልተረዳም። ተካዩ በፍሬው የሚደሰትበት ምንም መንገድ የለም! ሽማግሌው ለቄሳሩና ለእኛ ለመጪው ትውልድ መጨነቅ፣ በሰውና በተፈጥሮ መካከል ስላለው ልዩ ግንኙነት ጠቃሚ ትምህርት ያስተማረበት ሚድራሽ ላይ የተመሠረተ ታሪክ።

የእድሜ ክልል: አንደኛ ክፍል

“በፍሬው ባንደሰትም ዛፍ መትከል ፋይዳ ይኖረዋል? አንድ ሽማግሌ ለቀጣዩ ትውልድና ለዓለም ቀጣይ ህልውና በማሰብ በለስን ይተክላል። እግረ መንገዱንም ቄሳሩን አድርያኖስን እንዲሁም አንባቢዎችን ገና በሚመጣው መልካም ነገር ላይ እምነት ስለማሳደርና ስለ ትዕግስት ጣፋጭ ፍሬዎች ጠቃሚ ትምህርት ያስተምራል።
አባቶቼ እንደተከሉኝ እኔም ልጄን እተክላለሁ።
[እንደ ባቢሊ፣ ታዓኒት 23 1]

ምንጩን ማወቅ
“”በለስ የተሞላ ቅርጫት”” የተባለው መጽሐፍ በጥንታዊ ሚድራሽ ላይ የተመሰረተ ነው፦ በንጉሱ አድርያኖስ ተግባር ወደ ጦርነት ሄዶ በእርሱ ላይ ያመፀችውን አገር ለመውጋት ከዘማቾቹ ጋር ሄደ። በመንገድ ላይ የበለስን ተክል የሚተክል ሽማግሌ አገኘ። አድርያኖስም እንዲህ አለው፦ አንተ አርጅተሃል ግን ቆመህ ተጨንቀህ ለሌሎች ትለፋለህ? (ሽማግሌው) ጌታዬ ንጉሥ ሆይ፣ እየተከልኩ ነው አለው። ከደረስኩበት የተከልኩትን ፍሬ እበላለሁ። ካልሆነ ደግሞ ልጆቼ ይበላሉ። እርሱም (አድርያኖስ) በጦርነቱ ውስጥ ሦስት ዓመታት አሳልፎ ተመለሰ። ከሶስት አመት በኋላ ያንኑ አዛውንት በእዛው ቦታ አገኘው። ያው ሽማግሌ ምን አደረገ? – ቅርጫት ወስዶ በሚያማምሩ የበለስ ፍሬዎች ሞልቶ ወደ አድርያኖስም ቀረበ። በፊቱም፦ ጌታዬ ንጉሥ ሆይ፥ ከባሪያህ ተቀበል አለው። በእግርህ ስትሄድ ያገኘኸኝ ያው ሽማግሌ ነኝ። አንተም ለምንድነው ቆመህ ተጨንቀህ ለሌሎች የምትለፋው ብለኸኝ ነበር። ይኸው ቦታው አድርሶኝ የተከልኩትን ፍሬ እንድበላ አብቅቶኛል። እነዚህም በቅርጫት ውስጥ ያሉት ላንተ ስጦታ ናቸው። ወዲያውም አድርያኖስ ለአገልጋዮቹ፡- ቅርጫቱን ከእርሱ ውሰዱና ወርቅ ሙሉት አላቸው፤ እነርሱም እንዲሁ አደረጉ። (ሚድራሽ ታንሑማ፣ ክዶሺም 8)”

ታሪኩን ተከትሎ የሚመጣ ቪዲዮ

איך להפוך למשפחה של קוראים?

የተሰራጩት ቅጂዎች:

46,500

ማተሚያ ቤት:

תכלת

የስርጭት ዓመት:

תשפ״ד 2023-2024, 2018 2017-2018